Wednesday, March 18, 2015

አርበኞች ግንቦት7 – በህወሓት ላይ የሚቀርቡ ተቃውሞዎች ሁሉ ወደ እምቢተኝነት ይደጉ!

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyየኢትዮጵያ ሕዝብ በአለፉት 23 ዓመታት በህወሓት ዘረኛ አገዛዝ የደረሰበት ስቃይ እንዲቀንስ፤ ገዢዎቹ ከጫንቃው እንዲወዱ፤ ህወሓትን አውርዶ የሚፈልጋቸው መሪዎችን በነፃነት እንዲመርጥ ሲጠይቅና አቤቱታ ሲያሰማ ቆይቷል። በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሕዝብ ምኞት የሚሳካ መስሎ የታየ የነበረ ቢሆንም በአገዛዙ አረመኔዓዊ እርምጃ ተሰናክሏል። ከጥቂት ዓመታት ወዲህ “ድምፃችን ይሰማ” የሚሉ አቤታዎች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች መምጣት ጀምሯል – “ድምፃችን ይሰማ ሙስሊሞች”፣ “ድምፃችን ይሰማ ኦርቶዶክሶች”፣ “ድምፃችን ይሰማ መምህራን”፣ “ድምፃችን ይሰማ ተማሪዎች”፣ … ወዘተ። በተለይ ሙስሊም ወገኖቻችን በተደራጀ መንገድ “ድምፃችን ይሰማ” እያሉ ሲወተውቱ ሦስት ተከታታይ ዓመታት አልፈዋል። ወገኖቻችን “ድምፃችን ይሰማ” በማለታቸው ተደብድበዋል፣ ታስረዋል፣ ተገድለዋል።
አቤቱታ የሚሰማ ጆሮ የሌለው አገዛዝ ሲገጥም ምን ይደረጋል? ለአቤቱታ አቅራቢው ያለው ምርጫ ከሁለት አንድ ነው። ወይ አቤቱታን እርግፍ አድርጎ ጥሎ በደልን ተቀብሎ “እህህ !” እያሉ መኖር፤ አሊያም “በቃኝ፣ እንቢ አልገዛም” ማለት፤ ሦስተኛ ምርጫ የለም።

የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት በአሜሪካ የደረሰባቸው ተቃውሞ በጠ/ሚ ሃይለማርያም፣ ጌታቸውን አሰፋ፣ ኢሳትና ሌሎች ሃይሎች የተቀነባበረ ነው አሉ

imagesየሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት በአሜሪካ የደረሰባቸው ተቃውሞ በጠ/ሚ ሃይለማርያም፣ ጌታቸውን አሰፋ፣ ኢሳትና ሌሎች ሃይሎች የተቀነባበረ ነው አሉ
መጋቢት ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በአንድ ኢትዮጵያዊ ከፍተኛ ተቃውሞ ያገጠማቸው አቶ አብዲ ሙሃመድ ተቃውሞውን ያቀነባበሩት ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ የደህንነት ሹሙ ጌታቸው አሰፋ፣ ኢሳት ፣ ግንቦት7 እና የኤራትራ መንግስት በጋራ በመሆን ነው ሲሉ አካራ ኒውስ በተባለው የግል ዌብሳይታቸው ላይ በሶማልኛ ባወጡት ረጅም ጽሁፍ ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ተቃውሞውን ሲያሰማ የነበረውን መኮንን የተባለውን ሰው ስም ከፊት በማስቀደም፣ መኮንን ጌታቸው አሰፋ ሃይለማርያም ብለው ጽሁፋቸውን ይጀምሩና ኢሳት ከጀርባ ሆኖ ሲያቀናብር እንደነበር ያትታሉ።

መድረክ ከምርጫ ጋር በተያያዘ የተፈጸሙ ጥቃቶችን ዘርዝሮ አቀረበ

መጋቢት ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተለያዩ ክልሎችን የሚሸፍነው ሪፖርት፣ በዜጎች ላይ የተፈጸሙ ዝርዝር ጥቃቶችን አቅርቧል።  በትግራይ ክልል በአጽቢወንበርታ ምርጫ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመድረክ ዕጩ ተወዳዳሪ የሆኑት አቶ ወ/ገብርኤል ኃይሉ የዕጩነት መታወቂያ እንደያዙ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ የአስር ወራት የእስራት ቅጣት ተፈርዶባቸዋል፡፡
 “በቆላ ተንቤን ወረዳ በወርቅ አምባ ምርጫ ክልል የክልል ም/ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ የሆኑት አቶ ብርሃን ንጉስ ተክለእግዚም በተመሳሳይ ሁኔታ የዕጩነት መታወቂያቸውን እንደያዙ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ የሶስት ዓመት የእስራት ቅጣት ተፈርዶባቸዋል፡፡”
” ወ/ሮ ቤራይ ገብሩ የሚባሉ በሁመራ ምርጫ ክልል የክልል ም/ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ ደግሞ ከታሰሩ በኋላ ተፈትተዋል፡፡ የአቶ ወ/ገብርኤል ኃይሉ የእርሻ መሬትም ተነጥቆ የሕወሐት አባላት ለሆኑ ወጣቶች ተሰጥቷል፡፡ “
በሁመራ ምርጫ ክልል የአረና/መድረክ አባል የሆኑት ቄስ ህሉፍ ካህሳይና በቆላ ተንቤን የአረና/መድረክ አባል የሆኑት  አቶ ዜናዊ አስመላሽም በፖሊስ፣ በኢህአዴግ ካድሬዎችና በአከባቢ ሚሊሺያዎች ተደብድበው ለከፍተኛ ጉዳት ተዳርገዋል፡፡

Saturday, March 7, 2015

ተዋቂው ጋዜጠኛ አለምንህ ዋሴ የህዝቡን ትግል ተቀላቀለ !


2_1812

ጋዜጠኛው በኢትዮጵያዊነቱ አያሌ በደሎች እንደ ተፈጸሙበት ያወጋል ! በተለይ ይላል ጋዚጠኛ አለምነህ ዋሴ ፍትህ እኩልነት በሌለባት ሃገሬ ጋዜጠኛ ርዩት ዓለሙ ላይ የተፈፀመው ኢሰባዊ ድርጊት ከሁሉም በላይ ከህሊናው ሊጠፋ የማይችል ዘግናኝና አረምኔያዊ ድርጊት መሆኑን ይገልጻል ። ጋዜጠኛው ልጆቹን ከማሳደግ ባሻገር ሃገሩ ላይ ሲኖር ደስተኛ እንዳ ልነበረ በመጥቀስ ክእንግዲ አለ ጋዜጠኛ አለምንህ ዋሴ « ፍትህ እኩልነትና ነጻነት እስኪሰፍን » ሃገር አለኝ ብዬ ፊቴን ወደ ኢትዮጵያ አልዞርም ብሏል ። ጋዜጠኛው ከየትኛውም የፖለቲካ ድርጀት ገለልተኛ ሆኖ ወገኑን ማገልገል እንዳልቻለና የገዢው ስረአት ወሬአቀባይ ሳይሆኑ ገለልተኛ ሆኖ በነጻነት ኢትዮጵያ ውስጥ ሰርቶ መኖር ለህልውና አደገኛ መሆኑን የራሱን ተሞክሮ በመጥቀስ ያብራራል።

Tuesday, March 3, 2015

”ፀረ-የኢትዮጵያ ታሪክነት’ነት ለምን? – ሁኔ አቢሲኒያ

Adwaአንድ ወቅት ሎሬት ጸጋዬ አንድ ስብሰባ ላይ የተጠየቁት ጥያቄ ትዝ ይለኛል። <<ስለ አፄ ቴዎድሮስ ሁል ጊዜ እያሞገሱ ለምን ይጽፋሉ?>> ተብለው ሲጠየቁ <<አይ ሌላውንማ የኢትዮጵያ ጠላቶች ይጽፉታል>> ነበር ያሉት።  ስሞኑን ሎሬት የተነበዩትን በገሃዱ ሕይወታችን እያነበብን ይሆን?
የህወሓት መስራቾች ለትግል በረሃ ከወጡበት ዘመን ምሮ፣ ቂም ቋጥረው ደም የተቃቡት ከደርግ አገዛዝ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሐገሪቱ ታሪክም ጋር እስኪመስል ድረስ በአፍራሽ ፕሮፓጋንዳ ላይ ተጠምደው እንደነበር ይታወሳል፤ በተለይም ለአፄ ምኒሊክ ስምና ስራ ያላቸው ጥላቻ ወሰን አልባ ነው። የድርጅቱ ‘ማኔፌስቶ’ የተዋቀረበት ጭቃና ማገርም በሐገሪቱ የአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ቡድን የበላይነት (ጭቆና) መኖሩን አውስቶ የአንድነትና የዘመናዊት ኢትዮጵያ አባት ዳግማዊ ምኒሊክን አንኳሶና አጠልሽቶ አዲስ ታሪክ መፍጠሩ የትላንት ትዝብት ነው።

አየር ሐይልን ከድቶ በይፋ ግንቦት 7ን የተቀላቀለው ሻለቃ አክሊሉ መዘነ ታናሽ ወንድም ሠይፈ መዘነ በማዕከላዊ ቶርች እየተደረገ መሆኑ ታወቀ

“ተዋጊ አውሮፕላኖች የኮንትሮባንድ ማመላለሻ ሆነዋል” በማለት የኢትዮጵያ አየር ሃይልን እና የገዢውን ፓርቲ አካሄድ በመቃወም ግንቦት 7ን መቀላቀላቸው የሚታወሠው ሻለቃ አክሊሉ መዘነ ቤተሠቦች አደጋ ላይ ይገኛሉ፡፡
ኮተቤ 02 አካባቢ በተለምዶ ቆርቆሮ ሠፈር እየተባለ በሚጠራው ስፍራ የሚኖሩት የሻለቃ አክሊሉ ቤተሠቦች ሻለቃ አክሊሉ በተለያዩ ምክንያቶች ግንቦት 7ን መቀላቀላቸውን ተከትሎ በቤተሠቡ ላይ የሚካሄደው ምርመራ እና ክትትል በገዢው ፓርቲ የደህንነት ሀይሎች ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በተለይም በታናሽ ወንድሙ ሠይፈ መዘነ በማዕከላዊ ቶርች እየተደረገ እንደሚገኝ ተገልጧል፡፡