Thursday, January 29, 2015

ትግሬ ብሎ ነገር…

አንዳንዶቻችን ኢህአዴግ ያጠፋውን ጥፋት ለትግሬና ለትግራይ ጠቅልላችሁ ለምን እንደምታስረክቡ አይገባኝም፡፡አንዳንዶቻችሁማ ብሶባችኃል ትንሽ ዕድልና ብዙ ሃይል ብታገኙ መታወቂያ እያያችሁ ይሄን ህዝብ ብትረፈርፉት ደስታችሁ መሆኑን ትሰብካላችሁ፡፡ወንድሞቼ ኢህአዴግ ከመላው ብሄረሰቦች የተውጣጡ እንከፎች የመሰረቱት ማህበር እንጂ ትግሬና ትግሬያዊያን የፈጠሩት ክስተት አይደለም፡፡
የአማራ መሬት ምርጥ ሰዎችን እንደማፍራቱ አዲሱ ለገሰ፣ታምራት ላይኔ፣አለምነው መኮነንን የመሰሉ በሰው ደም ሻወር የሚያምራቸው ሰዎችን አፍርቷል፡፡የኦሮሞ ህዝብ ታሪክን በብርሃን ያደመቁ ጀግኖችን እንደመውለዱ አባዱላ ገመዳ፣ሙክታር ከድር፣ግርማ ብሩን የመሰሉ አስረፍራፊዎችን ለኢህአዴግ አዋጥቷል፡፡ጉራጌ ካሱ ኢላላን፣ሲዳማ ሽፈራው ሽጉጤን፣ወላይታ ሃይለማሪያምን አሳድጓል፡፡ሶማሌ ፣ጋምቤላ ፣ሀረር ውስጥ ለተፈጠሩ እልቂቶች ምላጭ ሳቢዎቹ ፣አሰቃዮቹ ራሳቸው በአከባቢው ተወልደው ያደጉ ሳዲስቶች አልነበሩም?

በኢትዮጵያ መንግስት በጥብቅ የሚፈለጉ 3 አርቲስቶች

Kibebeew geda

ከሮቤል ሔኖክ
እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ ሃሳብን በነፃነት ያለመግለጽ መብት አለመከበሩ ያጠቃው ጋዜጠኞችን ብቻ አይደለም። አርቲስቶችም ጋዜጠኞች ከሚከፍሉት መስዋእትነት ያልተናነሰ ትግል እያደረጉ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳለመታደል ሆኖ የሃሳብን የመግለጽ ነጻነት በመገደቡ ዛሬ እንደ ታላቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙና ተመስገን ደሳለን ያሉ ጋዜጠኞች ያልሆነ ክስ ተልጠፎባቸው በእስር ላይ ይገኛሉ። የእነዚ ታላላቅ ጋዜጠኞች ‘ወንጀል’ መንግስት እንደሚለው ሳይሆን የሕዝብን በደልና ብሶት ማሰማታቸው ብቻ ነው።

መታረም የሚገባዉ ማነዉ? ርዕዮት አለሙ ከቃሊቲ እስር ቤት

በግል የህትመት ዉጤቶች አማካኝነት በሀገሬ ዉስጥ የምመለከታቸዉን ችግሮች ለህዝብ ማቅረብና እንደዜጋም መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸዉን ሀሳቦች መጠቆም ከጀመርኩ አምስት አመታት አለፉ፡፡ የመጀመሪያ ፅሑፌን ያዘጋጀሁት ” “ስህተቶችን” ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶችና የስህተት ማረሚያ እርምጃዎች” በሚል ርዕስ እንደነበረ አስታዉሳለሁ፡፡ በዚህም ፅሑፍ የፕሬስ፣የፖለቲካፓርቲዎች ምዝገባና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተመለከቱ አዋጆች የወጡበት ምክንያትና እንደሀገር የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ለመዳሰስ ብሎም ኢህአዴግ ከስህተቶቹ እንዲታረም ለመምከር ሞክሬያለሁ፡፡

Ryotየኢህአዴግ ሰዎች በአንድ የገዢዉ ፓርቲ ልሳን በሆነ ድረገፅ አማካኝነት የማስጠንቀቂያ ይዘት ያለዉ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ከላይ ከጠቀስኩት የመጀመሪያ ፅሁፌ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በአዲስፕሬስ ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ተቀጥሬ መስራት ስጀምር ግን ሁኔታዉ እየባሰ መጣ፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም አዳማ ላይ ከተለያዩ ሚዲያዎች ለተዉጣጣን ጋዜጠኞች የሰጠዉን ስልጠና ከተካፈልኩ በኋል ከስልጠናዉ ጋር በተያያዘ ለህትመት ያበቃሁት ፅሁፍ ኢህአዴጎችን በእጅጉ አስቆጣቸዉ፡፡ በመሆኑም ወደቢሮአችን ተደዉሎ ከኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የተደወለ መሆኑ ከተገለፀ በኋላ ለጽሑፌ ምላሽ የላኩ በመሆኑ በፍጥነነት እንድናወጣዉ ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጠን፡፡ ምላሻቸዉን ለማዉጣት የእነሱ መደወልም ሆነ ትዕዛዝ አስፈላጊ አልነበረም፡፡

Tuesday, January 27, 2015

በኖርዌይ ኦስሎ እንግሊዝ ኢንባሲ ፊት ለፊት በደማቅ ሁኔታ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

norway 1
norway ethiopian
norway ethiopian
norway ethiopian 3
                             ቀን፡ 01/26/2015
በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ በወጣቶች ክፍል አስተባባሪነት በዛሬው እለት ሰኞ( January 26,2015) በኖርዌ ኦስሎ በእንግሊዝ ኢንባሲ ፊት ለፊት በኖርዌይ የሚኖሩ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በህብረት ሁነው ከ14፡00 _15፡00 ስዓት ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፉ በደማቅ ሁኔታ አካሄዱ።
የሰልፉ ዋና አላማ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሃፊ የነበሩትንና የሰባዊ መብት ተቆርቋሪ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በአረመኔው፣ ሰው በላ፣ ጨቋኙና በአንምባ ገነኑ የወያኔ ፋሺስታዊ ቡድን የአለም አቀፍ የሰባዊ መብትን ህግ በጣሰ መንገድ በሰኔ 2014 ታፍነው እስኳሁንም ድረስ ፍትህ ተነፍገው በእስር ቤት መታሰራቸውን ለመቃወም እንዲሁም የእንግሊዝ መንግስት አርበኛው የነጻነት ታጋዩ አንዳርጋቸው እየተፈጸመበት ያለውን ተፈጥሮአዊና ዲሞክራሲያዊ የመብት ጥሰት ተመልክቶ ከእስር ሊወጣበት የሚችልበትን አፋጣኝ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ ለማሳሰብ ነው።

Sunday, January 25, 2015

በኢትዮጵያ ውስጥ አገዛዙ የሚያካሂደው አፈና ተጠናክሮ ቀጥሏል – ሸንጎ

ለአስቸኳይ ስርጭት
shengoየኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) እራሱን በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የጫነው አገዛዝ በተቃዋሚ ድርጅቶች ላይ አፈናውን አጠናክሮ የቀጠለ መሆኑን ለመረዳት ችሏል።  በነገው ዕለት (ጥር 17 ቀን 2007 ዓ. ም) በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ (አንድነት) አስተባባሪነት ሊደረግ ከታሰበው ሰላማዊ ሰልፍ አስቀድሞ የአገዛዙ የፀጥታ ኃይሎች ቢያንስ አራት የአንድነት ፓርቲ የአመራር አባላትን ማሰራቸውን ሸንጎ ተገንዝቧል።  ከታሰሩት ውስጥ፦
  1. አቶ አሥራት አብርሃም – የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ
  2. አቶ ሰለሞን ሥዩም – የአንድነት የ”ሚሊዮኖች ድምጽ” የኢዲቶሪያል ቦርድ አባል
  3. አቶ ስንታየሁ ቸኮል – የአዲስ አበባ የወጣቶች ክፍል ሃላፊ
  4. አቶ ነዋይ ገበየሁ – የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ም/ሃላፊ እንደሚገኙበት ለመረዳት ተችሏል።

Thursday, January 22, 2015

የሕሊና እስረኛዋ ርዕዮት ዓለሙ ልደት: ከርዕዮት በጎውን እንቅና !

ይድነቃቸው ከበደ
ዙርያን በመመልከት ካለንበት መጀመር ለምንም ነገር የተሻለ ነው፤ ከቤተሰብህ፣ከጓደኛ፣ከማህበረሰብ ራስን ለመረዳት እና ትርጉም ያለው ሥራ ለመስራት፣ በጎውን ለማድረግ ብንቀና ለስኬታችን ቀላል መንገድ ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል “በጎውንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቀችሁ ማን ነው ? በማላት በጴጥ.መ.ምዕ 3ቁ 13 ላይ ተገልፆ ይገኛል ፡፡
1310 ቀን በእስር እያሣለፈች የምትገኘው፣የተወዳጇ የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ የልደት በዓል ፣እጅግ በጣም ደስ በሚል ሁኔታ በድምቀት ተከብሯአል፡፡ በልደት ቀኗ ተዋቂ ግለሰቦች፣የፓለቲካ ፓርቲ መሪዎች እና አባላት፣ጋዜጠኞች፣የማህበራዊ-ድረ ገፅ ዋንኛ አንቀሳቃሾች፣ ጓደኞቿ እና ቤተሰብ በመገኘት የበዓሉ ተካፋይ ለመሆን ችለዋል፡፡ በቦታው በመገኘት ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም፣ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ፣ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እንዲሁም አቶ በላይ በፍቃዱ በተሰጣቸው አጭር ደቂቃ በመጠቀም ለርዮት መልካ ልደት ከመመኘት በላፈ ፣አስደማሚ ንንግር አድረገዋል፡፡

“ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም” – በኢትዮጵያ የመገናኛ-ብዙሃን ነጻነት ላይ የሚፈፀም የመብት ጥሰት (የሂውማን ራይትስ ዋች መግለጫ)


Jail
እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 2015 ዓ.ም. ማጠቃለያ
የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) እ.ኤ.አ. በ2010 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ 99.6 በመቶ የፓርላማ መቀመጫን ካሸነፈ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት ሃሳብን የመግለጽ ነጻነትን እና መረጃ የማግኘት መብትን በመገደብ በግል መገናኛ-ብዙሃን ላይ እያሳደረ ያለውን አሉታዊ ተጽዕኖ አባብሶታል፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ ቢያንስ 60 ጋዜጠኞች ሃገር ለቀው የተሰደዱ ሲሆን ሌሎች 19 ጋዜጠኞች ደግሞ በእስር ላይ እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡፡ መንግስት በደርዘኖች የሚቆጠሩ ህትመቶችን ዘግቷል፤ እንዲሁም አብዛኛዎቹን የቴሌቪዥን እና የሬድዮ ስርጭቶች በቁጥጥሩ ስር በማድረግ ኢትዮጵየዊያን የሀገር ውስጥ የፖለቲካ ጉዳዮችን በተመለከተ ነጻ መረጃ እና ትንታኔ የሚያገኙበትን እድል አጣቧል። በግንቦት 2007 በሚካሄደው ምርጫ መገናኛ-ብዙሃኑ ህዝቡን በወሳኝ ጉዳዮች ላይ በማስተማርም ሆነ መረጃ በመስጠት ረገድ ቁልፍ ሚና ሊጫወቱ ይችሉ ነበር፤ እንዲሁም የመከራከሪያ መድረክ በመሆን ሊያገለግሉ ይችሉ ነበር፤ ይሁን እንጂ መንግስት በሃገሪቱ ላለው ብቸኛ የበላይነት የግሉን መገናኛ-ብዙሃን እንደ ስጋት አድርጎ በመውሰድ የግሉን መገናኛ-ብዙሃን፣ ነጻ ጋዜተኝነትን እና ተቺ ትንታኔን ለማጥፋት የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ላይ የሚገኝ ሲሆን ይህም የከፋ ውጤት አስከትሏል።

Tuesday, January 20, 2015

ካድሬዎች በየሜዳው የምርጫ ካርድ በግዳጅ እየሰጡ ነው

election
 በአዲስ አበባ ከተማ ከ2 ምርጫ በፊት በ0 የተሸነፈው የገዢው ስርዓት ባለፈው ምርጫ 96.6% አሸንፍኩ ማለቱን ተከትሎ ምርጫው መሳቂያ እንደሆነበት ብዙዎች ሲተቹበት የቆየ ጉዳይ ነው:: በባለፈው ዓመት ምርጫ ብዙ ሰው “ብንመርጥም ስለሚጭበረበር ግዜዬን አላጠፋም” በሚል ካርድ ያልወሰደ ሲሆን ዘንድሮ በግድ እንዲወስዱ እየተደረገ ነው::
የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ያነጋገሯቸው ምንጮች እንደሚሉት ስርዓቱ ያዘጋጃቸው ካድሬዎች በየቤቱ እየሄዱ የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ እያስገደዱ ሲሆን ከታክሲና አውቶቡስ መውረጃ ቦታዎች ላይ ወንበር እና ጠረጴዛ አስቀምጠው አላፊ አግዳሚውን በግድ የምርጫ ካርድ እንዲውስድ እያስገደዱት ነው::

Monday, January 19, 2015

(ይናገራል ፎቶ) ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ኤርትራ በርሃ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን ታጋዮች ጋር

የኢሳቱ ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ኤርትራ ከሚገኙ የኢትዮጵያውያን ታጋዮች ጋር ቆይታ አድርጓል:: ጋዜጠኛው እዚያው የሚገኙትንና ብረት አንስተው አሁን ያለውን የሕወሓት አስተዳደር ለመጣል ከሚታገሉት ታጋዮች ጋር የተነሳውን ፎቶዎች ይናገራል ፎቶ ስንል አቅርበንላችኋል::

Saturday, January 17, 2015

የተመስገን ደሳለኝ ወንድም በ8 ፖሊሶች ተደበደበ * ጠ/ፍ/ቤት የተመስገንን ይግባኝ ውድቅ ኣድርጎ የ3 ዓመት ፍርዱን ኣጸና

(ዘሐበሻ) ጋዜጠኛ ተመስገን ያቀረበው ይግባኝ ውድቅ ተደርጎ የ3 ዓመት እስሩ እንዲፀናበት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወሰነ ። ከዚህ ፍርድ ቀደም ብሎ ወንድሞ ታሪኩ ደሳለኝ በ8 ፖሊሶች ክፉኛ ተደበደበ።
ታሪኩ ደሳለኝ በፌስቡክ ገጹ ጉዳዩን እንዲህ ገልጾታል:-
Temesgen Desalegn behindbarክልከላና ድብደባ በዝዋይ እሰር ቤት
ለስምንት አንድን ሰው በደም እስኪታጠብ ድረስ በርግጫ፣ በጥፊና በሰደፍ መደብደብ፣ በእጁ ላይ የሚገኝውን ብርና መፃሀፍ መንጠቅ፣ ስልኩን መስበር…. ይህ ድርጊት በሌሊት አንድ ሰው ላይ በሌቦች የተፈፀመ ሳይሆን ትላንት ከረፋዱ በ 5 ሰዓት ላይ በዝዋይ እስር ቤት ግቢ ውስጥ በኔ ላይ የተፈፀመ ነው፤
ነገሩ እነዲህ ነው የሆነው፣ እንደልማዴ ዝዋይ የደረስኩት በማለዳ ነው፡፡ የያዝኩትን ስንቅ አስፈትሼ እንደጨረስኩ የሬዲዬ መገናኛ የያዘ መቶ አለቃ እንደሆነ የሚገልፅ ማዕረግ ያለው ወታደር እየገላመጠኝ “ለምን መጣህ?” አለኝ፤ “እዚህ የታሰረ ወንድም አለኝ እሱን ለመጠየቅ ነው” ስል መለስኩ፡፡ ቀጥ ብለህ ወጣ ተከተለ “አንተ ወንድምህን መጠየቅ አትችለም” ሲለኝ “ምክኒያቱ ይነገረኝ” ብዬ ብናገር ከጉዳይም አልቆጠረኝም “እሺ እኔ ባልገባ እንኳን ያመጣሁት ምግብን አድርሱልኝ” ብል ስሚ አጣሁ፡፡ አንገቴን ደፍቼ ልወጣ ስል መቶ አለቃው በሬዲዬ እያወራ አንድቆም በእጁ ምልክት ሲሰጠኝ ልገባ ነው ብዬ ደሰ አለኝ፡፡

Thursday, January 15, 2015

ሰማያዊ ቲሸርት የለበሱ ወጣቶች ከስላሴ በዓል ላይ ተባረሩ

• ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ‹የፈራ ይመለስ› የሚል ቲሸርት አስለብሶ ሲበጠብጠኝ ሰንብቷል፡፡›› የየካ ክፍለ ከተማ ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ
• ‹‹ገዥው ፓርቲ ጥላውን የማያምንበት ደረጃ ላይ ደርሷል!›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ
semayawiዛሬ ጥር 7/2007 ዓ.ም የዓመቱን የስላሴ በዓል ለማክበር አራት ኪሎ የሚገኘው ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን የተገኙ ወጣቶች ሰማያዊ ቲሸርት በመልበሳቸው በፖሊስ እንደተባረሩ የአይን እማኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ ‹‹ያመነ፣ የተጠመቀ ይድናል!›› የሚል ሰማያዊ ቲሸርት የለበሱትን ወጣቶች ቲሸርቱን እንዲያወልቁ ሲጠይቅ ወጣቶቹ አናወልቅም በማለታቸው ከበዓሉ ማባረሩን እማኞቹ ገልጸዋል፡፡ ከተባረሩት ወጣቶች መካከል አብዛኛዎቹ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚገቡትንና የሚወጡትን አማኞች በማስተባበር ላይ እንደነበሩ የተገለጸ ሲሆን የተባረሩት ወጣቶች ይታሰሩ አይታሰሩ የታወቀ ነገር የለም፡፡

Monday, January 12, 2015

የአርቲስት አስቴር በዳኔና ሳሞራ ፍጥጫ በደደቢት በረሃ

…አርቲስት አስቴር በዳኔ ከተቀመጠችበት ወደፊት ወጥታ ማይኩን ስትጨብጥ ፍርኃት ቢጤ እንደወረራት ከመጀመሪያው ያስታውቃል፡፡ ‹‹በጣም ነው የሚያስፈራው፤›› በማለት የጀመረችውን አስተያየቷን የያዘችውን ማስታወሻ እያነበበች አስተያየት መስጠት ቀጠለች፡፡
‹‹ይህንን ዕድል ተመቻችቶልን በቴሌቪዥን ስናየው የኖርነው ታሪክ ለማየት ስለቻለን እጅግ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል፡፡ በፊት የነበረኝ ያልተጨበጠ አመለካከት በመረጃ የተደገፈ ሆኗል፤›› በማለት ሐሳቧን ቀጠለች፡፡ ‹‹እውነትን መናገር እወዳለሁ፡፡ የሐሳብ ነፃነትም አለ፡፡ በእርግጥ የፖለቲካ ሰው አይደለሁም፤›› በማለት ታዳሚዎችን ፈገግ ያሰኘች ሲሆን፣ በሒደትም የፍርኃቷ መጠን እየቀነስ የመጣ ይመስላል፡፡

ወያኔ ኢትዮጵያን አፍርሶ ወደ ጉሬው ለመግባት

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት     ቅዳሜ ጥር ፪ ቀን ፪ሺህ፯  ዓ.ም.                         ቅፅ ፫ ፣ ቁጥር ፰
የመጨረሻ መሠናዶውን እያደረገ ነው
· የትግሬ-ወያኔዎች ከተለያዩ ጎሣዎች እና ነገዶች ሰዎችን መልምለው እና አደራጅተው፣ እንዲሁም የወታደራዊ፣ የደህንነት፣ የአደረጃጀት፣ የአመራር እና የቁጥጥር ሥራ የሚሠሩ የትግሬ-ወያኔዎች መድበው በከፍተኛ ሚሥጢር ኢትዮጵያን የማፈራረስ ሤራ እየተዶለቱ መሆኑን በተጨባጭ መረጃዎች አረጋግጠናል።
ethiopia-map
የትግሬ-ወያኔ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን በመበታተን፣ የትግራይ ረፑብሊክ መመሥረት መሆኑን በ1968 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ፕሮግራሙ መሠረት ላለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ያደረገው ጉዞ ያሣያል። በጉዞው የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ታሪክ ክዶ በመቶ ዓመት መገደቡን፣ የትግሬ-ወያኔ መሪዎች እና አባሎች በተደጋጋሚ በጻፉዋቸው መጻሕፍት እና በየአጋጣሚው ባደረጉዋቸው ንግግሮች ለሕዝብ ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። «ኤርትራ በኢትዮጵያ በቅኝ ግዛትነት የተያዘች ናት፤ ስለሆነም ሻዕቢያ የሚያካሂደው የመገንጠል እና የነፃነት ጥያቄ ተገቢ እና ትክክል ነው።» ብለው፣ ከሻዕቢያ በላይ ሻቢያ ሆነው፣ የትግራይን ልጆች የጦር ማገዶ በማድረግ ኤርትራን ማስገንጠላቸው ማንም ሊያስተባብለው የማይችለው ሃቅ ነው።

የማለዳ ወግ … የኢትዮጵያ አፈር የጠራው ጠቢብ የክብር ጉዞ ፍጻሜ !

መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላል …!
image-9d7f88cbdecd3715a84ff1e923f19a265e6c 3ebc9096e18394f23acdc537c8db-V_resized_1አርአያነታቸው ፋና ወጊ ሆኖ እያለ ብዙ ያል ተነገረላቸውን ዶር በርናርድ ብሬድሊ አንደር ሰንን ባዘከርኩበት የማለዳ ወጌ የጠቢቡን ህይዎት ከጃማይካ እሰከ አሜሪካ ለመቃኘት መሞከሬ እውነት ነው ። ዛሬም የምቀጥለው ከዚያ ለጥቆ ያለውን የዶር በርናርድን አፍሪካና ኢትዮጵያ ያደረሰውን መንገድ ሲሆን እንደ መግቢያ በአንድ የጥምቀት ዋዜማ ጎንደር ከዶር በርናርድና ከባለቤታቸው ከሲስተር እማዋይሽ ገሪማ ጋር የነበረንን አጭር ቆይታ በጨረፍታ በመቃኘት መጀመሩን ልቤ ፈቅዷል … የፈቀዳችሁ ተከተሉኝ !

ገዢ ቢሰባ ለመሬት አህያ ቢሰባ ላራዊት

ቢኒያም ግዛው ከኖርዌይ ኦስሎ
ይሄ ምርጫ መቼስ ስንቱን ያስታውሰናል?በደርግ ዘመን እናቶች ወንድ ልጃቸውን ከየጉያቸው እየተነጥቁ እና እየታፈሱ በጦርነት ሲማገዱ ወንድ ልጅ ላለመውለድ. . . ትዝም አላለሽ ወይ የክፉ አመቱ ላንቺና ለልጅሽ ያለቀ ስንበቱ ማህጸኔን ዝጋ ይቅር ምን አባቱ በእንባ እየዳከርሽ ብለሽ ያልሽበቱ። እያሉ ፈጣሪን ወንድ ልጅ እንዳይሰጣቸው የለመኑትን ቤቱ ይቁጠራቸው። የአፈሳና የሀገራችንን አንድምታ ለመረዳት ከሰሞኑ በየከተማዎችና ጎዳናዎች ያለው የድብደባ የአፈሳና የሞት ፍርሀት ድባብ ተቀባብሎ ለቃታ የተዘጋጁ ጥይት በእያንዳንዱ ሰላማዊ ዜጋ ጆሮ ስር ተደግኖ እንደሚራመድ በቀላሉ መረዳት ይቻላል።
. . . ጭቃ ከማቡካት ጀምሮ አብሬው ያደኩት ጓደኛዬ ስሙ ጌታቸው ይባላል። እንዴት እንደምንዋደድ እንደምንተሳሰብ እና እንደምንመካከር አትጠይቁኝ። በቃ ጌቾ ምርጥ ጓደኛዬ ነው።

ሰሚ ያጣ ጮኸት ከካርቱም – አጥናፉ መሸሻ

በመላው አለም ለምትገኙ ኢትዮጽያዊያኖች ሁሉ    ፤ በተለያዩ ግዜያት  ሰብአዊ  መብታችን  ይከበር ዘንድ ፤  ከምድር ሱዳን የሲቃ ጮኸታን ሰምታችሁ  በተቻላችሁ መጠን ትታደጉን ዘንድ ደጋግመን በፁሁፍ አሰምተናል ፤ እንሆ  በአሁኑ ሰአት ወያኔ ከምንግዜውም በላይ በከፋ መልኩ  ፤ ካርቱም ውስጥ  ስደተኛውን አንደተለመደው እያሳፈሰ ፤ ወዳልታወቀ እስር ቤት እያሳወሰደ ይገኛል ፤ በተለይ ጀዋዛት እየተባለ በሚገኘው እስር ቤት ውስጥ ፤ በሸህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ታጉሮው ይገኛሉ ፤ ከእነዚህም ውስጥ ለልደት ደሮ ለመግዛት ገበያ የሔዱ እህቶቻችን ከነደሮቸው ፤ ልደትን መድሀኒአለም ቤተክርስትያን አክብረው የሚመለሱ ነጭ የለበሱ ወገኖች  እስር ቤቱን ሞልተውታል ፤ በተጨማሪ ዴም እየተባለ ከሚጣረው ሰፈር ውስጥ አንድ ወጣት ሀለፎም አዲሱ ተካልኝ የተባለ የአንገት መስቀሉን በጥሰው መኪና ላይ ጭነው እስር ቤት አጎረውት ይገኛል ፤ መታወቂያ ለማውጣት እድሜው የማይፈቅድ ወጣት ሳይቀር  ያለ አንዳች እርህራሔ አስር ቤት ይገኛል ፤ ይህን ወጣት እንደምሳሌ ተጠቀምንበት እንጅ በርካታ ወጣቶች መኖራቸውን አናሳስባለን;;

“አንዱ ቡድን ሌላዉን ጥሎ ለማለፍ የሚያደርገዉ ግብግብ ዉጤታማ ሊሆን አይችልም” ትንሳኤ ኢህአፓ

Tensaye
ድር ቢያብር አንበሳ ያስር!
እኛ የትንሳኤ ስብስብ በተለያዩ ጊዜያት በጽሁፍ፤ በሬዲዮ ብሎም በቴለቪዥን መስኮትያለንን አላማ ለኢህአፓ አባላቶችና በተለያዬ ምክንያት ከድርጅቱ ለወጡ እንዲሁም በድርጅቱ ዉስጥ ለመታገል ለሚፈልጉ ታጋይ ኢትዮጵያዉያን ሁሉ በተደጋጋሚ አሳዉቀናል፤ ዛሬም እንደገና ወደፊት ድርጅቱን ለማጠናከር ተገቢ ናቸዉ ብለን ለምንመኛቸዉና አጥብቀን ስለምንታገልለት ዴሞክራሲያዊ አካሄድ መተንተኑ ተገቢ ነዉ እንላለን፤፤
አሁንም ቢሆን የኢህአፓ ከሁለት መከፈል እጅጉን አሳዝኖናል፤ አበሳጭቶናልም፤ ይህነዉ የሚባል ወይም መሰረታዊ የሆነ የአላማ፤ የርእዩተ አለምና የራእይ ልዩነት ሳይኖር፤ ብዙ ጓዶች ዉድ ህይወታቸዉን የገበሩበት፤ የቆሰሉለትና የደሙለትን ድርጅት፤ ሃላፊነት በጎደለዉና ከምክንያት ይልቅ በስሜት ተገፋፍቶ፤ በግብር ይዉጣ መልክ ድርጅቱን መከፋፈልና ትግሉን አደጋ ላይ መጣሉ፤ በትንሳኤ ስር የተሰባሰብነዉን ጓዶች አንገብግቦናል አሳስቦናልም፤ ለዚህም ነዉ እራሳችንን አሰባስበንና አጠናክረን በዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነት የሚመራና፤ ከሁላም በላይ ለሰፊዉ ህዝብ የበላይነት የሚታገል የጋራ አአንድ ኢህአፓ ለማሰባሰብ ያለምነዉ፤፤

Friday, January 9, 2015

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፖለቲካዊ ደባ አንድነት ከመስመር አይወጣም! – አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ!
በየትኛውም የአለም ክፍል በተለያየ አጣራርና ስያሜ ቢሰጣቸውም ምርጫን ለማስፈፀም በሕግ የሚቋቋሙ ተቋማት ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ተቋማት በአንድ ሀገር ዘላቂ ለሆነ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ለዴሞክራሲዊ ስርዓት ግንባታ ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ፡፡ እንደ ኢትዮጵያ በአንባገነን ስርዓት ውስጥ ላሉ ሀገሮች ደግሞ ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ያላቸው ሚና ከምንም በላይ ከፍተኛ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራው ምርጫ ቦርድ ይህን የመሰለ ግዙፍ ተግባር እንዲያከናውን፣ የሕዝብ እና የሀገር አደራ እንዲወጣ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ የዚህ ተቋም አሰራር በተቋቋመለት ዓላማ፣ ሕግ እና አለም አቀፍ መስፈርት መሠረት ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ዴሞክራሲያዊ እና በህዝብ ዘንድ ተአማኒነት ያለው መሆን ይጠበቅበታል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀደሙት አሠራሮችና ውሳኔ አሰጣጦች በበርካታ ኢትዮጵያውያን እና አለም አቀፍ ታዛቢዎች በአሉታዊ ጎኑ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

በመላው ሀገሪቱ ለምትገኙ ለአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በሙሉ! ወሳኝ የትግል ምእራፍና ወሳኝ ሰዓት ላይ እንገኛለን !!!

ኢህአዲግና ምርጫ ቦርድ በስውር ከተደራጁ ህገ-ወጥ የማፊያ ቡድኖች ጋር በመሆን አይበገሬና በቆራጥ ሰላማዊ የነፃነት አርበኞች የተገነባውን አንድነት ፓርቲን ላለፉት ጊዜያት ፓርቲያችንን ለመበታተንና የህዝብ አለኝታነቱን በማሳጣት ከምርጫ ለማስወጣትና ሰላማዊ የትግል ሂደቱን ለማኮላሸት ያልፈነቀሉት ድንጋይ እንዳልነበረ፤..መላው ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያንና የአንድነት አባላት ሲከታተሉት የነበረ ሀቅ ነው፡፡ ……በኢህአዲግ የበላይነት የሚመራው ምርጫ ቦርድ፤….. በህወሀት ካድሬዎች ተቀባብሎ የሚሰጠውን አንድነትን ኢላማ ያደረገ ጥይት ለመተኮስ ወደኋላ አልተመለሰም፡፡ ….ከጥቂት የስርአቱ ተላላኪ በአንድነት ውስጥ የተሰገሰጉ ሰርጎ ገቦችና በገንዘብ የተገዙ የሀገርም ሆነ የወገን ፍቅር የሌላቸው ባንዳዎች ጋር በመደራጀት አንድነትን የመፈረካከስ ውጥናቸውን ለማሳካት በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ በጅተው ሲንቀሳቀሱ ሰንብተዋል፡፡

ለምን ወለድናቸው?። – ዳዊት ዳባ።

ፖሊስ የደብረ ማርቆስ ተማሪዎችን እየደበደበ ነው፡፡ የትናንትናው ተቃውሞ በኢሳትና በሌሎች ሚዲያዎች መተላለፉን ተከትሎ ‹‹ማን ነው ከኢሳትና ከሌሎች ሚዲያዎች ጋር እየተደዋወለ መረጃ የሚሰጠው?›› እንዲሁም ‹‹የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ካለ ተናገሩ›› በሚል ተማሪዎቹን አሳልፈው እንዲሰጡ ከፍተኛ ደብደባ እየፈጸመ መሆኑን ከቦታው የደረሰን መረጃ ይጠቁማል፡፡ ፖሊስ አሁንም ተማሪዎችን እየፈለገ እያሰረ መሆኑም ተገልጾአል ይላል የዛሬ ዋና ዜና።
deberemarcos-7ለምን ለሚልና ላልሰማ። ወያኔዎች አንድ ቀን ቀደም ብሎ ‹‹የአብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና በደብረማርቆስ የመለስተኛ ሁለተኛ እና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ (መሰናዶ) ተማሪዎች መስጠት ጀመሩ። ክርክሩን በኢሳት ራዲዬ የሰማን በሙሉ ምስክር ልንሆን በምንችልበት  ህፃናቱ  በሀሳብ  ሞግተው ግልፅ ሆኖ በሚታይ ሁኔታ የስርአቱን ካድሬዎች አሸነፏቸው። ያነሷቸው ጥያቄዎችና መከራከሪያዎች ፍፁም እውነትነት ያላቸው፤ ብስለት የተሞላባቸውና ስክን ባለ ሁኔታ የሚቀርቡ ነበሩ።

ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ ዝዋይ የታሰሩ 16 የፖለቲካ እስረኞች ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ

ነገረ ኢትዮጵያ
• የሰማያዊ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ባልደረባ እንዳይጠይቁ ተከልክለዋል
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ በዝዋይ የፌደራል ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙ 16 የፖለቲካ እስረኞች ባልታወቀ ምክንያት ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ፡፡
temesgen1ዛሬ ታህሳስ 28/2007 ዓ.ም የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ም/ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ የገናን ዋዜማ ዝዋይ ከሚገኙ እስረኞቹ ጋር ለማሳለፍ ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ዝዋይ አቅንተው የነበር ቢሆንም ሊጠይቋቸው ያስጠሯቸው የፖለቲካ እስረኞች ‹‹በማንኛውም አይነት ሰው መጠየቅ አይችሉም፡፡ ምግብም አይገባላቸውም፡፡›› ተብለው ሳይጠይቁ ለመመለስ ተገደዋል፡፡
ጠያቂዎቹ ‹‹የመጠየቅ መብት አለን›› በሚል ወደ ውስጥ ለመግባት ግፊት በማድረጋቸው ፖሊሶች ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ አበበ ቀስቶ፣ ናትናኤል መኮንን፣ በቀለ ገርባ፣ ጄኔራል አሳምነው ጽጌና ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጨምሮ ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው የተከለከሉትን የ16 የፖለቲካ እስረኞችን ስም ዝርዝር አሳይተዋቸዋል፡፡

ፍትሕ አያረጅም! የኢትዮጵያና የአርሚኒያ ትግል -ኪዳኔ ዓለማየሁ

መግቢያ፤
Justiceኢትዮጵያንና አርሚኒያን ከሚያመሳስሏቸው ጉዳዮች አንደኛው የአንድ ዓይነት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት የእምነት መሠረት (ዶግማ) ተከታዮች ያሉባቸው ሐገሮች መሆናቸው ነው። በዚህ ጽሑፍ የማተኩርበት ተመሳሳይነት ግን ሁለቱም ሐገሮች በከባድ የጦር ወንጀሎች ተጠቅተው እያንዳንዳቸው ቢያንስ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ የተጨፈጨፈባቸው መሆኑ ነው። ሌላም እጅግ አስጸያፊ ግፍ የተፈጸመባቸው ሐገሮች ናቸው። በተጨማሪም፤ ሁለቱን ሐገሮች ያቀራረባቸው ሌላው ጉዳይ በኦቶማን ዘመነ መንግሥት፤ ከቱርኮች ግፍ በመሸሽ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት መልካም ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት 40 አርመኖች ኑሯቸውን በሐገራችን መቀጠላቸው ነው።

የግልና የ«ብሄር» ነፃነት በኣቶ ገብሩ ኣስራት እይታ

ኣምሃ ኣስፋው
«ሉኣላዊነትትና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ» የተሰኘው የኣቶ ገብሩ መፅሃፍ ከፍተኛ ተቀባይነትና ኣድናቆት እንዳተረፈ በየድረ ገፁ ተወስቷል። መፅሃፉ በኣማርኛው ጥራትም ሆነ በይዘቱ ጥልቀት ሊደነቅ የሚገባው ይመስለኛል። እርግጥ ብዙ የፊደል ግድፈቶች ኣሉበት። ይህ ግን፣ የኣርታኢዎች ስህተት ብቻ ሳይሆን፣ መቀምሮች (Computers) ማንም ሳያዛቸው በራሳቸው ፊደሎችን የመቀያየር ጠባይ ስላላቸውም ጭምር ነው። ይህ መፅሃፍ የደረሰን ከወያኔ/ህወሃት ኣባል እይታ ቢሆንም የዘመኑን ታሪክ ለማወቅ እጅግ ጠቃሚ ይመስለኛል። ሁኔታው ሲፈቅድ፣ ኢትዮጵያዊያን ልጆች ከሚማሩባቸው መፃህፍት ኣንዱ ቢሆን ከተለያዩ ኣቅጣጫዎች በሚመጡ ሃሳቦች የታነፁ ዜጎችን ለማፍራት ይጠቅማል የሚል እምነት ኣለኝ።
የኣቶ ገብሩን መፅሃፍ በኣማርኛው ጥራትና በይዘቱ ጥልቀት ባደንቀውም፣ የኣንድምታውን ትክክለኛነትም ሆነ የጭብጡን እውንነት እቀበላለሁ ማለቴ ኣይደለም። የዛሬው ፅሁፌም ምክንያት ከማይስማሙኝ ኣስተሳሰባቸው ኣንዱን ለመተቸት ነው፤ በንግግር ነፃነት ስለሚያምኑ ትችቴ ቅር እንደማያሰኛቸው በማመን።
Gebru Asrat
ኣቶ ገብሩ ባለማለት፣ የማለትን ጥበብ የተካኑ ፖለቲከኛ ይመስላሉ። የኣፄ ቴዎድሮስን የጀግንነት ኣሟሟት ሲተርኩ፣ ጠላቶቻቸውን፣ እንግሊዞችን፣ እየመሩ ያመጡት ኣፄ ዮሃንስ መሆናቸውን ይዘሉታል። የኣፄ ምኒልክንና የጣሊያኖችን ውል ደጋግመው ሲያትቱ፣ ጣሊያኖች ኤርትራን በኣፄ ዮሃንስ ዘመን ያልያዟት ለማስመሰል ይሞክራሉ። በሻብያና በኢትዮጵያ ህዝብ መሃከል በተደረገው የመጨረሻ ጦርነት፣ ከምእራብ እስከምስራቅ፣ ከሰሜን እስከደቡብ ያለውን ህዝብ ጀግንነት ሲያሞግሱ፣ ሸዋን እንዳልነበረ ሁሉ ይዘሉታል። በምርጫ 97 የቅንጅትን ኣባል ማህበሮች እንቅስቃሴ ሲገልፁ፣ የመኢኣድ ኣስተዋፅኦ እንዳልነበር፣ እነ ኣቶ ሃይሉ ሻውል ደግሞ እንዳልተፈጠሩ ለማድረግ ሞክረዋል። በደፈናው «ነባር ፖለቲከኞች» ይሏቸዋል። ኣድሃሪ፣ ፊውዳል፣ ነፍጠኛ፣ ትምክህተኛ፣ ምናልባትም እንደ ቀስተ ደመና የምሁራን ሳይሆን የደንቆሮዎች ስብስብ ከሚል ኣስተሳሰብ ብዙም የራቁ ኣይመስለኝም።
እነዚህ የቀድሞ ባለስልጣኖች ስልጣናቸውን ሲነጠቁና ጥቅማቸውን ሲነፈጉ የሚያሰሙት የ«ተሳስተን ነበር» ጩኸት ይገርመኛል። እንዲያውም የጥላሁንን ዘፈን ያስታውሰኛል።

ለመላው የክርስትና ኃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፥ – ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፪ሺህ፯ኛ የልደት በዓል አደረሳችሁ!
moreshነገ ኢየሱስ ክርስቶስ በምድራችን በአካል የተገለጸበትን ፪ሺህ፯ኛ ዓመት እናከብራለን። እግዚአብሔር ወልድ በምድር በአካል ከእኛ ጋራ በታየበት ዘመን ያስተማረን ትልቁ ቁምነገር ፍቅርን ነው። በተቃራኒው እኛ የዘመኑ ኢትዮጵያውያን በመካከላችን ፍቅር ጠፍቶ እንበጣበጣለን። በስደት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሌላው ቀርቶ በእምነቱ ሥፍራ እንኳን ሰላም ካጣ ቆይቷል። የዚህ ሁሉ ብጥብጥ እና ፍቅር መጥፋት ምንጩ የትግሬ-ወያኔ እና እሱን መሰል ፀረ-ኢትዮጵያ ዓላማ ያላቸው ድርጅቶች እና ልሂቃን ናቸው። ስለዚህ እኒህን የጥፋት ኃይሎች በጋራ ትግላችን ግስጋሴያቸውን ልናቆመው ይገባል። ክርስቲያኖች ከኢየሱስ ክርስቶስ ምሣሌ መማር ካልቻልን እና ካልተፋቀርን መከራችን ይረዝማል፣ ሥቃያችንም አያባራም። የትግሬ-ወያኔ እና መሰል አጋሮቹም እንደሠለጠኑብን ዘመናት ይቆጠራሉ።

የኢትዮጵያ አፈር የጠራው ጠቢብ፣ የድሆች አባት ዶ/ር በርናርድ ተለየን ! -ነቢዩ ሲራክ

የማለዳ ወግ …የድሆች አባት ዶ/ር በርናርድ ተለየን !
* የኢትዮጵያ አፈር የጠራው ጠቢብ
*” ክብር ሞቱ ለሰማዕት ”

(ጸሐፊው ነብዩ ሲራክ)
(ጸሐፊው ነብዩ ሲራክ)
ዛሬ የምናዘክረው ሰው የኢትዮጵያ አፈር ፍቅር ጠርቶት ለጉስቁል ተገፊው ደሃ የሀገሬ ሰው ህይዎት ትንሳኤ ተግቶ ለውጥ ስላመጣ  ጠቢብ ነው። ዝካሬ ታሪኩ ቢያስተምረን ፣ አርአያ ሰብዕናው ግብአት፣ ተሞክሮ ቢሆነን ፣ ህይዎት ንብረቱን በእኛው ቀዬ ስላፈሱሰ ትጉት ሀኪም ነው ! ነፍሳቸውን ይማር ብለን ለሰሩት ስራ ክብር በመስጠት እናዘክራቸዋለን!  ዶክተር በርናርድ አንደርሰን ይባላሉ ! በርናርድ ዛሬ አይሰሙም ፣ አያዩንም …
የዶር በርናርድን እረፍት ያረዳችኝ መነኩሴዋ እናቴ ሀዘኑ ጎድቷት ” ልጀዋ ዋርካችን ተገረሰሰ እኮ ፣ የድሆች አባትና ጠዋሪ መድሃኒታችን አጣንኮ … ” ነበር ያለችኝ … ያልጠበቅኩት ነበርና ድንጋጤው መላ አካሌን ወረረው  ። የእንባ ሳግ እየተናነቃት ሃዘኗን ያጋራችን እናቴን ከማጽናናት ባለፈ ምንም ማለት አልተቻለኝም! እናም ስለ ጠቢቡን የድሆች አባት ዶር በርናርድ አንደርሰን ላዘክር በተጎዳ ስሜት ብዕሬን ሳነሳ ጠቢቡ በሰጡት የኑዛዜ ቃል መሰረት ቀብራቸው በሚወዷት ሀገረ ኢትዮጵያ ምድር ይሆን ዘንድ በተናዘዙት መሰረት ሊፈጸም ተቃርቧል ። ውድ ባለቤታቸው የአርበኛው ደራሲ ገሪማ ታፈረ ልጅ ከሲስተር እማዋይሽ ገሪማም  ከምድረ አሜሪካ የዶር በርናርድን ቃል ለመፈጸም ዛሬ እኩለ ቀን አ.አ ይገባሉ  !  ጥቂት ስለድሆች አባት በርናርድ አንደርሰን ላጫውታችሁ …

የበደል ድርድር – የቅጥፈት ውድድር። (ከሥርጉተ ሥላሴ)

/ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/
Andargachew 1እንደ ሰው አለመሆንን ፍንትው አድርጎ ባሳዬው የሰሞናቱ የበደል ድርድር አብዛኛው የጭድ ክምር ሆኖ ነው እኔ በግሌ ያገኘሁት። በሌላ በኩል ግን ይህንን እጅግ የወረደ የቴሌቪዥን ቅንብር አይቶ ወያኔ መላእክ ሌላው ዓለም ጭራቅ ብሎ ብይን የሚሰጥ ሰው ይገኛል ብሎ መገመት እራሱ እውርነት ነው። ቀድሞ ነገር ለሰብዕዊ መብት ክብር ህጋዊነትን ለማብሰር የሃሳብ ነፃነት፤ የመደራጀት ነፃነት፤ የዕምነት ነፃነት፤ የመሰብሰብ ነፃነት፤ የመምረጥና የመመረጥ ነፃነት ዕውን መሆን አላባቸው – በጥቂቱ። ይህን ስለአደረጉ አስሮ – ደብድቦ – አፍኖና አሰቃይቶ „ሰብዕዊ መብታቸው ተጥበቆ ተዝናንተው ያልተጠዬቁትን ሳይቀር ተናገሩ¡“ ማለት እጭነት ነው። ለመሆኑ የወንድማቸውን ሁኔታ በአካል ተገኝተው ለማዬት ከሀገረ አሜሪካ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ የሄዱትን እህታቸውንስ ስለምን በ24 ሰዓት ባዕታቸውን ዬእትብት መንደራቸውን ለቀው እንዲወጡ አደረገ ወያኔ? ይህም የወያኔ የነፃነት ገነት ተብሎ ሊወደስ ይሆን¡?

መታረም የሚገባዉ ማነዉ? ርዕዮት አለሙ ከቃሊቲ እስር ቤት

በግል የህትመት ዉጤቶች አማካኝነት በሀገሬ ዉስጥ የምመለከታቸዉን ችግሮች ለህዝብ ማቅረብና እንደዜጋም መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸዉን ሀሳቦች መጠቆም ከጀመርኩ አምስት አመታት አለፉ፡፡ የመጀመሪያ ፅሑፌን ያዘጋጀሁት ” “ስህተቶችን” ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶችና የስህተት ማረሚያ እርምጃዎች” በሚል ርዕስ እንደነበረ አስታዉሳለሁ፡፡ በዚህም ፅሑፍ የፕሬስ፣የፖለቲካፓርቲዎች ምዝገባና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተመለከቱ አዋጆች የወጡበት ምክንያትና እንደሀገር የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ለመዳሰስ ብሎም ኢህአዴግ ከስህተቶቹ እንዲታረም ለመምከር ሞክሬያለሁ፡፡
Ryotየኢህአዴግ ሰዎች በአንድ የገዢዉ ፓርቲ ልሳን በሆነ ድረገፅ አማካኝነት የማስጠንቀቂያ ይዘት ያለዉ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ከላይ ከጠቀስኩት የመጀመሪያ ፅሁፌ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በአዲስፕሬስ ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ተቀጥሬ መስራት ስጀምር ግን ሁኔታዉ እየባሰ መጣ፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም አዳማ ላይ ከተለያዩ ሚዲያዎች ለተዉጣጣን ጋዜጠኞች የሰጠዉን ስልጠና ከተካፈልኩ በኋል ከስልጠናዉ ጋር በተያያዘ ለህትመት ያበቃሁት ፅሁፍ ኢህአዴጎችን በእጅጉ አስቆጣቸዉ፡፡ በመሆኑም ወደቢሮአችን ተደዉሎ ከኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የተደወለ መሆኑ ከተገለፀ በኋላ ለጽሑፌ ምላሽ የላኩ በመሆኑ በፍጥነነት እንድናወጣዉ ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጠን፡፡ ምላሻቸዉን ለማዉጣት የእነሱ መደወልም ሆነ ትዕዛዝ አስፈላጊ አልነበረም፡፡ የዝግጅት ክፍላችን አንድ ጽሑፍ የቀረበበት አካል ምላሹን በዚያዉ በተፃፈበት የህትመት ዉጤት ላይ ማስነበብ እንደሚችል በህግ የተደነገገ መሆኑን ከማወቁም በላይ የትኛዉንም አይነት ሀሳብ ለማስተናገድ ክፍት ነበርና ምላሻቸዉን በጋዜጣችን ላይ ታተመ፡፡ በዚህ ብቻ ግን አልተገቱም፤ በወቅቱ የገዢዉ ፓርቲን ሀሳብ በማቀንቀን ይታወቁ የነበሩት እንደ ዳጉ ኢትዮጵያና ሰነድ ያሉ ጋዜጦች ሀሳቦቼን በሃሳብ መምታት ባለመቻላቸዉ ይሁን ባለመፈለጋቸዉ ተራ ዘለፋዎችን ያወርዱብኝ ጀመር፡፡

ባለቤት የሌለው መሬት – ቤጌምድር! (የመከላከያ ሰራዊት በትግራይ እና አማራ ተዋጊዎች መካከል ሰፈረ (ከዚያስ?))

begemedeir
(ዳዊት ከበደ ወየሳ)
ሉም ኢትዮጵያዊ ስለዚህ አካባቢ እኩል ግንዛቤ ላይኖረው ይችላል:: በመሆኑም ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ስለዚህ አካባቢ ታሪካዊ ዳራ ማሳየት አስፈላጊ ሆኗል:: እናም በታሪክ መንኮራኩር ትንሽ ወደኋላ መሄድ ሊኖርብን ነው::
 ይህ የሰሜን አውራጃ ከጥንት ጀምሮ ቤጌምድር ተብሎ የሚታወቅ ሲሆን በራሱ መሪዎች ይተዳደር የነበረ ስፍራ ነው::

በጎንደር አርማጭሆ የተቀሰቀሰው ግጭት ሊበርድ አልቻለም

10923573_1560615314186107_7573440129440943485_nኢሳት ዜና :-ባለፈው ሳምንት ታጣቂዎች በከባድ መሳሪያዎች በመታጀብ በጎንደር አርማጭሆ ውስጥ <<ሶረቃ>> የሚባለውን አካባቢ ወደ ትግራይ ለማካለል በወሰዱት እርምጃ የተነሳው ግጭት እስካሁን ሊበርድ እንዳልቻለ በስፍራው የሚገኘው የኢሳት ወኪል ያጠናቀረው ሪፖርት ያመለክታል።

Wednesday, January 7, 2015

አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል – አቶ ኪዳኔ አመነ – የመድረክ ወጣት አመራር

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በተመለከተ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን የማፅዳት ሃላፊነት ከተወጣ በኋላ ገዢው ፓርቲ ጥርሱን የነከሰበት ይመስላል፡፡ ብዙ ፈተና እየገጠመው ነው፡፡ በምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እስከማድረግም ደርሰዋል፡፡
በኔ እምነት አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ብዙ ርቀት የሄደ ይመስለኛል፡፡ ትእግስታቸው አደንቃለሁ፡፡ ፓርቲው በውስጡ ከጥቂቶች በቀር በዙዎቹ ቁምነገር የሚያስቡ የምናከብራቸውና የምንወዳቸው ጥሩ ሰዎች አሉት፡፡ ትርጉም ያለው የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ ጥቂት ፓርቲዎች አንድነት አንዱ ነው፡፡

ታሪክ ለመስራት እንዘጋጅ – አቶ ተክሌ በቀለ የአንድነት ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር

አንድነት ፓርቲ የኢህኣዴግን ምንነት ላላመኑ ወገኖች ለማጋለጥ በትጋትና በስሌት ሲሰራ ቆይቷል፡፡እየሰራም ነዉ፤እዚህ ደርሷል፡፡ “የሆደ ሰፊዉን ምርጫ ቦርድ” ሆድ በገሃድ አጋልጧል፡፡በነአሞራዉና ወዲ ቐሺ(በተጋሩ ሁሉ) ትግልና ሞት የሚቀልዱትን በህዝብ ፊት ወጥተዉ ዛሬም እንዲዋሹና ለኢትዮጵያችን የፖለቲካ ታሪክ እነማን ምን እንደሆኑ አንድነት ፓርቲ የበኩሉን ሚና ተጫዉቷል፡፡ ለኔ ከባድመ ዉሳኔና ልህዝቡ በወቅቱ ከተነገረዉ ጋር ይመሳሰላል፤ይጠጋጋል፡፡
ኢህኣዴግ ምርጫዉን እንደማይፈልገዉ፤ከፈለገዉም ለተለመደዉ ቀልዱ ከነማን ጋርና በምን ሁኔታ እንደሚፈልገዉ ፓርቲያችን ሶስተኛዉን (የአዉሮፓና አሜሪካ ታዛቢዎች የሌሉበት ምርጫ መሆኑን፤የህዝብ ታዛቢዎች የተበላሸ የምርጫ ሂደትና ፓርቲዎችን የማፈራረስ/የማዳከም ስራዎች) ነጥብ አስመዝግቧል፡፡

Monday, January 5, 2015

ዛሬ የወያኔው ፖሊስ ስለለቀቀው የአንዳርጋቸው ጽጌ አዲስ ቪድዮ ዙሪያ የተሰጡ አስተያየቶች

የሕወሓት አስተዳደር ፖሊስ ዛሬ ስለአንዳርጋቸው አዲስ ቪድዮ ለቋል:: በየሶሻል ሚዲያዎችም መነጋገሪያ ሆኗል:: በዚህ ዙሪያ ከሶሻል ሚዲያዎች የተለያዩ አስተያየቶችን ስለቪድዮው ሰብስበናል ያንብቧቸው:-
andargacew Tsige
የጆሜክስ ካሳዬ አስተያየት:-
ሌባና ፖሊስ የሚባለው የገዢው አገልጋይ የሆነው የፌዴራል ፖሊስ ፕሮግራም የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ቪዲዮ በማሳየት አሜሪካን የሚያስንቅ የምርመራ ሥልት አለን እንደ ሌባ ሻይ ሳንገርፋቸው ይናዘዛሉ በማለት የድፍረቱን (የድድብናውን) ልክ ሊያሳየን ሞክሯል፣ ይህ መራር ቀልድ በአስቀያሚ የማዕከላዊ ምርመራ ሂደት ውስጥ ያለፉትንና ቶርቸርን ያስተናገዱት ጓደኞቼን ሳስብ ድፍረቱ አሳምሞኛል ፤ጓደኞቼም በማዕከላዊ ቆይታቸው የታዘቡት ጥፍራቸው የተነቀለባቸውን ተማሪዎች ሳስብ እነዚህን መርማሪዎች እና ጋዜጠኞች በፍትህ አደባባይ አገኛቸው ዘንድ ዘወትር እናፍቃለሁ፤
ፕሮግራሙ አሜሪካን ሊያብጠለጥል የፈለገበት እና የጠቀሰወው ሰሞነኛው የቶርች ሪፖርት ኢትዮጵያም ተሳታፊ መሆኗን እንዳጋለጠ ዘንግተውት ይሆን ብዬ አልጠይቅም አንዴ ምንም አያመጡም አያውቁም ተብለን ተንቀናልና (ሕዝብን ከመናቅ ካለሆነ ከምን ይመነጫል?)፡፡

ዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ለአስራ አምስተኛ ጊዜ ተቀጠሩ

zone 9
በዛሬው እለት በካንጋሮ ፍርድ ቤት የቀረቡት የዛኦን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ከዚህ ሁሉ ኢ-ፍትሃዊ እስር በኋላም ቢሆን ከፊታቸው ላይ ሳቅና ፈገግታን ሊነጠቁ ያልቻሉ መሆኑ በግልጽ ለአምባገነኖች እና አሽከሮቻቸው አሳይተዋል:: በሙሉ ራስ መተማመን ስሜት እና በታላው ብሩህ መንፈሳቸውን ተላብሰው ካንጋሮ ፍርድ ቤት ይደረሱት ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን የአሸናፊነት ስሜት በፊታቸው ይነበባል::ፖሊስ ጉዳዩን የሚከታተሉ እና በፍርድ ቤቱ የተገኙትን ስልካቸውን እንዲያጠፉ ያደረገ ሲሆን በችሎት ክተሰየሙት ዳኛ አንዱ መቀየራቸውም ታውቋል:;እንዲሁም ፖሊስ ያሰራቸውን ጦማርያን እና ጉዳዩን ሊክታተሉ የመጡትን በአይን እንኳን እንዳይነጋገሩ ሲያዋክብ ታይቷል::

Friday, January 2, 2015

ግንቦት 7 – ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባል!

Ginbot 7 weekly editorialኢትዮጵያ ሀገራችን በታሪኳ ከአስከፊ የፈተና አረንቋ ውስጥ ተገፍታ የገባችበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ዜጎችዋ ከፋሽስት ኢጣልያ በከፋ ሁኔታ ይህ ቀረሽ የማይባል የመከራ መአት የወረደባቸውና እየወረ ደባ ቸው የሚገኝበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመን ወያኔ ብቻ ነው፡፡ እስር ቤቶች ሞልተው ተጨማሪ እስር ቤቶች መገ ንባት ከልማት ተቆጥሮ የሚፎከርበት ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የሀገሪቱ ብሄራዊ ባንክ ንብረት የሆ ነው ወርቅ በባሌስትራ ለውጦ እስከ መዝረፍ የደረሰ በጠራራ ፀሀይ የህ ዝብና የሀገር ሀብት ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ በጥቂቶች የሚዘረፍበት ዘመን ቢኖር የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የጅምላ እስር፤ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ ስደትና መፈናቀል፤ ይበልጡንም በታሪካችን ታይቶ በማያውቅ መልኩ ለሞት፤ ለእስር፤ ለመፈናቀልና ለስደ ት ምክንያቱ የተገኘንበት ዘውግ የሆነበት ዘረኛ ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡

አቶ በረከት እሱን መች ጠየቅንህ?

ከፍተኛ ይቅርታ ይህ ጦማር ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለው ተቆርጦ በመቅረቱ ታርሞ ቀርቧል።
ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ(ህወሃት)የተመሠረተበትን አርባኛ ዓመት ለማክበር ሽር ጉድ እየተባለ ባለበትና በመጠኑ ከፍተኛ የሆነ የሀገሪቱ የገንዘብ ወጭ ተደርጎ አስረሽ ምችው የሚደለቅበት ሰአት ላይ ያለን ሲሆን የዘድሮው በዓል አከባበር ደግሞ የተለየ ሆኗል አስቀድመው ነው የጀመሩት ያም ሆነ ይህ በዓሉ ለምን ይከበራል? የሚያከብረውስ ማን ነው? ብለን ስንጠይቅ ድርጅቱ በጫካ አሥራ ሰባት ዓመት በትረ ሥልጣኑን ከጨበጠ በኋላ በከተሞች ለሃያ ሦሥት ዓመታት ያህል የምሥረታ በዓሉን በከፍተ የገንዘብ ወጭ እያከበረ ዘልቋል።

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይግባኝ ለታህሳስ 30 ተቀጠረ * ዝዋይ እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ችሎቱን ተከታትሏል

Temesgen Desalegn behindbar
(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ያስገባው የይግባኝ ጥያቄን ለመስመት ስድስት ኪሎ የሚገኘው ፍርድ ቤት ተሰይሞ የነበረ ሲሆን ጉዳዩን ተመስገን እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ተከታትሏል::
ከ’ፍሪ ተመስገን ደሳለኝ” የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ዛሬ ታህሳስ 23/2007 ጠቅላይ ፍረድቤት በዋለው ችሎት የጋዜጠኝ ተመስገን ደሳለኝን ይግባኝ ከሰማ በኋላ ጉዳዩ ለይግባኝ ያስቀርባል አያስቀርብም የሚለውን ለመወሰን ለታህሳስ 30/2007 ዓ.ም ቀጥሮ ሰቷል፡፡

ግንቦት 7 – ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባል!

Ginbot 7 weekly editorialኢትዮጵያ ሀገራችን በታሪኳ ከአስከፊ የፈተና አረንቋ ውስጥ ተገፍታ የገባችበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ዜጎችዋ ከፋሽስት ኢጣልያ በከፋ ሁኔታ ይህ ቀረሽ የማይባል የመከራ መአት የወረደባቸውና እየወረ ደባ ቸው የሚገኝበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመን ወያኔ ብቻ ነው፡፡ እስር ቤቶች ሞልተው ተጨማሪ እስር ቤቶች መገ ንባት ከልማት ተቆጥሮ የሚፎከርበት ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የሀገሪቱ ብሄራዊ ባንክ ንብረት የሆ ነው ወርቅ በባሌስትራ ለውጦ እስከ መዝረፍ የደረሰ በጠራራ ፀሀይ የህ ዝብና የሀገር ሀብት ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ በጥቂቶች የሚዘረፍበት ዘመን ቢኖር የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የጅምላ እስር፤ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ ስደትና መፈናቀል፤ ይበልጡንም በታሪካችን ታይቶ በማያውቅ መልኩ ለሞት፤ ለእስር፤ ለመፈናቀልና ለስደ ት ምክንያቱ የተገኘንበት ዘውግ የሆነበት ዘረኛ ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡

መልዕክት ከቂሊንጦ እስር ቤት! አብርሃ ደስታ

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
‹‹እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም›› አብርሃ ደስታ
እዚህ እስር ቤት ውስጥ በሽብር ስም የገባ ሰው በፈጠራ ወንጀል እንደገባ ነው የሚታመነው፡፡ ስለዚህ የሽበር ክስ ተመስርቶባቸው የታሰሩትን ሰዎች ማንም ወንጀለኛ አድርጎ አይመለከታቸውም፡፡ በእርግጥም አሸባሪ የለም፤ የፈጠራ ክስ ነው ያሳሰራቸው፡፡ አሸባሪ አለ ከተባለም እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም፡፡
ነጻ መውጣት ያለበት ቡድን አለ፣ እሱም ኢህአዴግ ራሱ ነው፡፡ እኔ አልታሰርኩም፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እስር የአዕምሮ ነው፡፡ እኔ አዕምሮየ አልታሰረም፡፡ ነጻ ሰው ነኝ፤ ውስጤ በጣም ነጻነት አለው፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡

አቶ በረከት እሱን መች ጠየቅንህ?

ከፍተኛ ይቅርታ ይህ ጦማር ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለው ተቆርጦ በመቅረቱ ታርሞ ቀርቧል።
ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ(ህወሃት)የተመሠረተበትን አርባኛ ዓመት ለማክበር ሽር ጉድ እየተባለ ባለበትና በመጠኑ ከፍተኛ የሆነ የሀገሪቱ የገንዘብ ወጭ ተደርጎ አስረሽ ምችው የሚደለቅበት ሰአት ላይ ያለን ሲሆን የዘድሮው በዓል አከባበር ደግሞ የተለየ ሆኗል አስቀድመው ነው የጀመሩት ያም ሆነ ይህ በዓሉ ለምን ይከበራል? የሚያከብረውስ ማን ነው? ብለን ስንጠይቅ ድርጅቱ በጫካ አሥራ ሰባት ዓመት በትረ ሥልጣኑን ከጨበጠ በኋላ በከተሞች ለሃያ ሦሥት ዓመታት ያህል የምሥረታ በዓሉን በከፍተ የገንዘብ ወጭ እያከበረ ዘልቋል።