እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፪ሺህ፯ኛ የልደት በዓል አደረሳችሁ!

ለዚህ መፍትሔው ፈጣሪያችን በፍርድ ቀን ሲመጣ የሚጠይቀንን ጥያቄዎች፥ ማለትም፦ “ስታመም ጠይቃችሁኛል? ስራብ አብልታችሁኛል? ስታረዝ አልብሳችሁኛል? ስታሠር አስፈትታችሁኛል? ስጠማ አጠጥታችሁኛል?” የተባሉትን ሠርክ እናስታውስ፣ በተቻለንም መጠን የሕይዎት መመሪያዎቻችን ለማድረግ እንጣር።
ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የክርስትና ኃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያንን እንኳን ለበዓለ-ልደቱ አደረሣችሁ፣ አደረሰን፣ ይላል። በዚህ አጋጣሚ ድርጅታችን ማስተላለፍ የሚፈልገው ጥሪ፦ ባለፉት ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት በትግሬ-ወያኔ ግፈኛ እና ናዚያዊ አገዛዝ ከምድረ-ገፅ የጠፉትን በቁጥር ከ፭(አምሥት) ሚሊዮን የማያንሱ ዐማሮች እናስታውስ። በገዛ አገራቸው ከቅኝ ተገዢዎች በከፋ መልክ ሰብዓዊ መብቶቻቸውን የተነጠቁትን ኢትዮጵያዊ ዐማሮች እንታደግ።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ይባርክ!
ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት
No comments:
Post a Comment