Wednesday, February 25, 2015

የባቡር ሃዲድ መስመር በሙስና ምክንያት ከደረጃ ውጭ እንዲሆን በመደረጉ የ124 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ደርሷል።

በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየተዘረፈ ነው – ሚኒስትሩ

* ከ30 እስከ 40% የግንባታ ወጭ ይዘረፋል!!

የኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪ ልማት ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ሃይሌ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን አጣሪ ቡድን ጋር ባደረጉት ውይይት ከመንገድ ስራ፣ ከባቡር መስመር ዝርጋታና፣ ከቤቶች ልማት ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየተዘረፈ መሆኑን አምነዋል።
የፀረ ሙስና ኮሚሽን ባካሄደው ጥናት በባቡር መስመር ግንባታ 2.3 ኪሜ የባቡር ሃዲድ መስመር በሙስና ምክንያት ከደረጃ ውጭ እንዲሆን በመደረጉ የ124 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ደርሷል። የአደጋ መከላከያ ብረቶች የተሰሩት ከወጣላቸው የጥራት ደረጃ በሶስት እጅ ያነሱ ሆነው በመገኘታቸው ጉዳዩ ለቦርድ ሰብሳቢው አርከበ እቁባይ ቢቀርብም ምላሽ ሳይሰጠው በመቅረቱ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የት እንደገባ ማወቅ አለመቻሉን ገልጿል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ዳኛ ቢኖር – ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም

የጎረቤት ኬንያ ዳኛ ለኬንያ መንግሥት አስፈጻሚው ክፍል ልኩን ነገረው፤ ሕገ መንግሥቱን በመርፌ አስተኝተህ ሕገ መንግሥቱን የሚጻረር ሕግ ለማውጣት አትችልም፤ ስለዚህም የሰነዘርኸውን የጉልበት ሕግ አንሣ፤ አለው፤ ዳኛ አይጥፋ! ሌላ ቢቀር ከጎረቤት ዳኝነትን እንስማ፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ዳኛ ቢኖር ስንት ጋዜጠኛ፣ ስንት የሃይማኖትና ስንት የፖሊቲካ መሪዎች ከየወህኒ ቤቱ ይወጡ ነበር! ሁላችንም እንደልባችን ሳንፈራ፣ ሳንፈራራ በሙሉ ነጻነት ችግሮቻችንን የወያኔን ጭቆና ጨምሮ ለመወያየትና መፍትሔዎችን ለመለዋወጥ የምንችልበት መድረክ፣ ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ራድዮና ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ ውስጥ ይኖረን ነበር፤ ስንት ሰው ሥራ ያገኝ ነበር፡፡
ከሁሉም በላይ በየመንገዱ ጠመንጃ የያዘ ሊያስፈራራን የሚሞክር ሆድአደር እያየን፣ እንደዚሁም በየጫካው ያሉትን እያሰብን ሰላማችንን ከምናጣ አበባውን ትተን፣ ሩዙን ትተን፣ የተወደደልንን ጤፋችንን እያመረትን አዲስ ኑሮ ብንጀምር የተሻለ ነበር፡፡
ግን አንድ እንቅፋት አለብን፤ እነዚህ ከየኪዮስኩ እውቀት ገዝተን አዋቂዎች ሆነናል የሚሉት እንትኖች እንመጀመሪያ ችግሩ እንዲገባቸው፣ ሁለተኛ መፍትሔው እንዲገባቸው፣ ሦስተኛ ጉልበትና እውቀት አንድ አለመሆናቸውን ብቻ ሳይሆን በጉልበት እውቀት የማይገኝ መሆኑን ማሳመን በረዶ እየወረደ የስሜን ተራራን መውጣት ነው፤ በረዶ ሳይኖር ወጥቼዋለሁ!

ከሜድትራኒያን ሞት ፊት የቆሙት ስደተኞች

0,,17150593_403,00ባለፈው የጎርጎሮሳውያኑ አመት የሜድትራኒያን ባህርን በጀልባ ለማቋረጥ ከሞከሩ 218,000 ሰዎች መካከል 3,500 መሞታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን አስታውቋል። በዚህ በተመሳሳይ መንገድ ወደ አውሮጳ ለመሻገር የሚሞክሩ ስደተኞች ቁጥር በአሳሳቢ ደረጃ በመጨመር ላይ ነው።
ሰለሞን መንግስቴ በሊቢያዋ የቤንጋዚ ከተማ ባለቤቶቹ ጥለውት የሄዱትን ቤት ይንከባከባል።አትክልት ይኮተኩታል። ግቢውን ያጸዳል። ሰለሞን በቤንጋዚ ብቻውን አይደለም። ባለቤቱ የዝና እዘዘው ቀን ቀን ከሰው ቤት ትሰራለች። ሰለሞን ስለ ወርሃዊ ደሞዙ ሲጠየቅ ፈገግ እያለ «በእውነት መቼ እንደሚከፍሉኝም አላወኩም።» ሲል ይመልሳል።
ሰለሞን ተወልዶ ካደገበት የጎንደር አካባቢ ወደ ሱዳን ገዳሪፍ የተጓዘው ለደላሎች አምስት ሺ የኢትዮጵያ ብር ከፍሎ በአስቸጋሪ የሌሊት ጉዞ ነበር። ጉዞውን ያመቻቹለት የኢትዮጵያ እና የሱዳን ህገ-ወጥ ደላሎች ነበሩ። «ጉዞው የሚጀመረው ለሊት ሰው በሌለበት ሰዓት በእግር ነው። የሚለው ሰለሞን መንገዱ ከሶስት እስከ ሰባት ቀናት ሊወስድ እንደሚችል ይናገራል።

Friday, February 20, 2015

ኢሕአዴግ የሕወሐትን የትግል ታሪክ የኢትዮጵያ ሕዝብ የነጻነት ትግል ታሪክ አካል ለማድረግ መሥራት ይገባዋል! በኒቆዲሞስ

ጽሑፌን በአንድ ገጠመኜ ልጀምር፡፡ በአንድ ወቅት ከጎንደር አገር ገና በአፍላነት ወጣትነት ዘመኗ ወደ ትግል ከገባች ታጋይና ከእናቷ ጋር ለመገናኘትና በአንድ ምሽትም ውይይታቸውን ለማድመጥ ዕድሉ ገጥሞኝ ነበር፡፡ የትግል ዘመኑ በድል ተጠናቆ፣ አገር ተረጋግቶ በነበረበት ሰዓት ልጃቸውን ለመጠየቅና ለሕክምና ከጎንደር የመጡ እኚህ እናት በወታደራዊ ዩኒፎርምና ማዕረግ ተንቆጥቁጣ ከአጠገባቸው ተቀመጠችውን የትናንትናዋን የበረሃ ፋኖ የዛሬዋን ወታደራዊ መኮንን ልጃቸውን በዛች ቅጽበትም ልክ እንደ ልጅነቷ ዘመን ዓይን ዓይኗን በናፍቆትና በስስት እያይዋት እንዲህ አሏት፡-
እንደው ራቴዋ አሁንማ ሥልጣን ስትይዙ፣ ወንበሩም ሲደላደል፣ ምቾቱም ድሎቱም ሲመጣ እኮ ረሳችሁን … እንደው ያ ከእናንተ ከልጆቻችን ጋር ያየነው መከራና ሥቃይ፣ እንባችን፣ እግዚኦታችንና ጸሎታችን የሚረሳ ነው፡፡ ገና ጡቶችሽ እንኳን በቅጡ ሳያጎጠጉጡ ከአጎትሽ ልጅ ጋር ጠፍተሸ ወደ በረሃ ገባሽ የተባለበትን ዜና በሰማሁ እለት ያፈሰስኩትስ እንባ ልጄ፡፡

‹‹ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ በምርጫ ሂደቱ እንዲቆይ አይፈልግም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት


ሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ከ200 በላይ ዕጩዎቹ በምርጫ ቦርድ ትዕዛዝ እንደተሰረዙበት የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በመላ አገሪቱ በተለይም በደቡብ ወሎ፣ በሰሜን ሸዋ፣ በወላይታ፣ በቤንች ማጅ፣ በምዕ/ጎጃም፣ በሲዳማ፣ በከምባታ፣ በጋሞጎፋ፣ አዲስ አበባ፣ በደቡብ ጎንደርና ጉጅን ጨምሮ በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች ከ200 በላይ ዕጩዎቹ አንድን ዕጩ ለመሰረዝ የሚያበቃ ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት ሳይኖር ‹‹ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ታዘናል›› በማለት ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤትና ለክልል ምክር ቤቶች ያስመዘገብናቸው ዕጩ ተወዳዳሪዎቹን በመሰረዝ ከምርጫው ውድድር ውጪ እንዲሆኑ እየተደረገ እንደሆነ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡

Monday, February 16, 2015

በሁለት ወር ውስጥ ከ15 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ የመን ገብተዋል(IOM)

 የመን ውስጥ ምላሱን የተቆረጠውን ሀፊዝ ጨምሮ 25 ኢትዮጵያዊያን ሆስፒታል ገብተዋል  ዮርዳኖስን መኪና ላይ አስረው መሬት ለመሬት ጎተቷት፣ (ሚሚ) ተደፈረች…ቃለ ምልልስ አለኝ (ግሩም ተ/ሀይማኖት) የመን ውስጥ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው በደል ከእለት ወደ እለት እየጨመረ መጥቷዋል፡፡ በጅቡቲ አድርገው ቀይ ባህርን ተሻግረው ወደ የመን የሚገቡትን ኢትዮጵያዊያንን በማገት 1000 እና 1500 የሳዑዲ አረቢያ ሪያል እና ከዛም በላይ ከወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲያስልኩ የሚያደርጉ አፋኞች መኖራችን ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ መግለጼ ይታወሳል፡፡

የአማራ ህዝብ ስቃይ እንዲያበቃ ወያኔን መቅበር ይኖርብናል

ዛሬ ወያኔ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ያፈናቀላቸው አማሮች የመጀመሪያዎቹ የወያኔዎች የጥቃት ሰለባዎች አይደሉም። የመጨረሻዎቹም አይሆኑም። ወያኔ ከነ ጸረ አማራ ፖሊሲው በስልጣን እስካለ ድረስና በአማራ ስም አማራውን እያፈኑ፣ እየሰለሉ ከወያኔ ፍርፋሪ እየለቀሙ ለመኖር የቆረጡ ከአማራው መሃል የወጡ ከሃዲዎች አማራውን መቆጠጠር እስከቻሉ ድረስ የአማራ ህዝብ መራቆት፣ ስደት፣ ውርደት፣ ሰቆቃና ሞት የማይለዩት ህዝብ እንደሆነ ይቀጥላል።

Wednesday, February 11, 2015

አበበ ገላው በአባዱላ ገመዳ 2 የውሸት ዲግሪዎች ግዢ ዙሪያ ማስረጃዎችን ለቀቀ

[Updated](ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ባለስልጣናት የሃሰት ዲግሪዎችን ከአሜሪካና አውሮፓ እንዲሁም ከቻይና እየገዙ እንደሚጠቀሙ በተደጋጋሚ እየተጋለጠ መሆኑ የሚታወስ ነው;; አበበ ገላው የዛሬ አንድ ወር ገደማ የዶ/ር ኮንተንጢኖስ በርሀን የሃሰት ዲግሪዎችን ያጋለጠ ሲሆን አሁን ተረኛው አባዱላ ገመዳ ናቸው ብሏል::
“ክቡር አፈጉባኤ አባዱላ ገመዳ አሜሪካ ሴንቸሪ ከሚባል የዲግሪ ወፍጮ ቤት የሃሰት ዲግሪዎች ገዝተው ጥቅም ላይ ማዋላቸው ተረጋገጠ” ሲል በፌስቡክ ገጹ ያስታወቀው አበበ ገላው ማስረጃዎቹን ዛሬ ለቋል::
አባ ዱላ ገመዳ የባችለር ዲግሪያቸውን እና የማስተር ኦፍ አርት ዲግሪያቸው ከአሜሪካው ሴንቸሪ ኮሌጅ በ2001 እና በ204 የገዙ ሲሆን ከ እንግሊዙ ግሪንዊች ዩኒቨርሲቲም ማስተር ዲግሪያቸውን እንዳገኙ ታውቋል::

የሰማያዊ አባላት በእጩነት እንዳይመዘገቡ ምርጫ ቦርድ እንቅፋት እየፈጠረ ነው

የምርጫ ቦርድ አባላት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ለእጩነት እንዳይመገቡ እንቅፋት እየፈጠሩ መሆኑን ፓርቲውን ወክለው በእጩነት ለመመዝገብ የቀረቡት የፓርቲው አባላት  ገልጸዋል፡፡ የቀድሞ አንድነት የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ የነበረውና በቅርቡ ሰማያዊ ፓርቲን የተቀላቀለው አቶ ስንታየሁ ቸኮል የትውልድ ቦታው በሆነው ምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ በእጩነት እንዳይመዘገብ የምርጫ ቦርድ ተወካዮች እንቅፋት እንደፈጠሩበት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
በእጩነት ለመቅረብ በአካባቢው ለሁለት አመት መኖር ወይንም ተወላጅ መሆን 
የሚጠበቅ ሲሆን አቶ ስንታየሁ በቦታው ተወላጅ በመሆኑ መመዝገብ የሚችል ቢሆንም ‹‹ምስክር አምጣ›› መባሉን ገልጾል፡፡ ‹‹ምንም እንኳ ተወላጅ በመሆኑ መመዝገብ እችል የነበር ቢሆንም ምስክር ስወስድም ምስክሮቹን ‹ችግር ከተፈጠረ እናንተ ናችሁ ተጠያቂ የምትሆኑት› እያሉ ምስክሮቹን እያሸሹ› እንዳልመዘገብ እንቅፋት ፈጥረውብኛል›› ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በሞጣ፣ በፍኖተ ሰላም፣ በባሌ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በተቀመጠው ጊዜ እንዳይመዘገቡ እንቅፋት እየተፈጠረባቸው ነው ተብሏል፡፡ አባላቱ ‹‹መረጃ አቅርቡ፣ ምስክር አቅርቡ›› ተብለው መረጃና ምስክር ይዘው ወደ ምዝገባ ጣቢያዎች ሲሄዱ ቢሮዎች ዝግ እንደሚሆኑና ‹‹አሁን ጥቆማ ነው፡፡ ምዝገባ አይደለም፡፡›› እያሉ እንደሚመልሷቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የጋራ ምክር ቤት አባል የሆኑ ፓርቲዎችን እጩዎች በስልክም ሳይቀር እየጠሩ እንደሚመዘግቡ፣ የሰማያዊ ፓርቲ እጩዎች ምዝገባ ጣቢያ ድረስ ሄደው ለመመዝገብ ሲያመለክቱ እንቅፋት ሲፈጥሩባቸው የብአዴን እጩዎች በአንድ ሰው ተወካይነት እንደሚመዘግቡ የሰማያዊ ፓርቲ የምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ፀኃፊ አቶ ሳሙኤል አወቀ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ሃይለማርያም ደሳለኝ የመለስን ሌጋሲ ክደው ከባላንጣቸው ከአቶ አርከበ ጋር ሽር ጉድ ማለታቸው የት ያደርሳቸው ይሆን? (ሪፖርታዥ)

HaileMariam
ምርጫ እና ድርጅታዊ ጉባኤ -አሁን ያለው አመራር ይቀጥላል
አቶ መለስ ያለሰብሳቢ በትነዋቸው የሄዱትና በዓይነ ቁራኛ የሚጠበባቁት የኢህአዴግ ባለሥልጣናት የሚተማመኑበት ድርጅት ሳያውቁት ፈርሷልና መክቶ የሚያድናቸው አይመስልም። ለምሳሌ እንዲህ ያለ ሁኔታ ሲፈጠር ተቃዋሚዎቻቸውን ማራገፍ የሚችሉበት የፓርቲው መዋቅር አካል የሆነው አንዱ መሣሪያ ድርጅታዊ ጉባኤና ምርጫ ነው። በዚህ ወቅት መተማመን ስለጠፋና ከመበላላት መሰንበት ስለተመረጠ በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ድርጅታዊ ጉባኤያቸው ከምርጫው በኋላ እንዲደረግ ተወስኗል። ባለፈው ከተደረገው 9ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባኤ በኋላ 10ኛው መደረግ የነበረበት ከምርጫው በፊት ነበር። አሁን ግን መች እንደሚደረግ የት እንደሚደረግ ሳይገለጽ በእንጥልጥል እንዲቀጥሉ ተደርጓል።

Thursday, February 5, 2015

የአንድነት አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ


መግለጫውን የ‹ቀድሞው አንድነት ፓርቲ› አፈ ጉባዔ የነበሩት አቶ አበበ አካሉ፣ ምክትል አፈ ጉባዔው አቶ ፀጋዬ አላምረው፣ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ እንዲሁም የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ሌሎችን በመወከል ሰጥተዋል፡፡
‹‹የምናምነው በሰላማዊ ትግል ብቻ ነው፡፡ ይህን ሰላማዊ ትግል ለመምራት ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ብቁ ነው ብለን በማመን ፓርቲውን ተቀላቅለናል›› ብለዋል በመግለጫው ላይ የተወከሉት አዲሶቹ የሰማያዊ አባላት፡፡
በዚህ መሰረትም በርከት ያሉ አመራሮችና አባላት በይፋ የሰማያዊ ፓርቲ የአባልነት ፎርም ሞልተዋል፡፡